ቀን፡ 27-02-2013
“የክህነት ተግባር እግዚአብሔርንም፤ ሰውንም ማገልገል ነው። እግዚአብሔርን ማገልገል ማለትም ካህናት መላእክትን መስለው በመዓልትና በሌሊት ለእግዚአብሔር የሚያቀርቡት ምስጋና ነው።
ሰውን ማገልገል ማለትም፡ ማስተማር፤ ማጥመቅ፤ ማቁረብ፤ መባረክ፤ መጠበቅ፤ መናዘዝ፤ መቀደስ፤ ማንጻት፤ ከኃጢአት መፍታት፤ ከእግዚአብሔር ማስታረቅ፤ በሞት ለሚለዩ ጸሎተ ፍትሐት ማድረግ፤ በጠቅላላው በትምሕርትና በትሩፋት ከርስቶስን መስሎ አብነት ሆኖ መገኘት ነው።”
(ማቴ.፩፫፡ ፩-፩፬ ፡ የሐ.ሥራ ፮:፬፡ ፳:፪፰-፫፩ ፡ ዮሐ. ፳:፪፩:፪፬፡ ፩ጢሞ. ፬:፩፫ ማቴ.፩፮:፩፱ ኤፌ.፬: ፩፩፡ ፩ጴጥ. ፭፡ ፩-፬)
ቀን፡ 10- 02-2013 ዕለቱ ዕለተ ሰንበት እሑድ ነበር።
ቦታ፡ ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን (United Kingdom)
በ03-02-02013 የቤተ ክርስቲያኑ ሰበካ አስተዳደር ጉባኤ (Management Committee) በገዛ ፍቃዳቸው ከሥራቸው በመልቀቃቸው ምክንያትና በተለይ 4 የምእመኑ ተወካዮች ሙሉ በሙሉ ስራቸውን አቁመው እቤታቸው በመቅረታቸው በምትካቸው አዲስ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ የሚያስመርጥ አስመራጭ ጉባኤ መምረጥ አስፈለገ።
በዚህ የምርጫ አፈጻጸም ላይ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪና ተከታዮቻቸው የሆኑ ካህናት የቤተ ክርስቲያኑን መተዳደሪያ ደንብና የቻሪቲ ሕግን በጣሰ ሁኔታ ለነሱ ሥጋዊ ጥቅም በሚያመች ሁኔታ ምርጫውን ለማካሄድ እንዳቀዱ ስለታወቀ በምርጫው መካሄድ የሁሉም ስምምነት ቢኖርም ነገር ግን ምርጫው እንዴት እንደሚካሄድና የሚመረጠው አዲስ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ ዓይነት አስመልክቶ የሃሳብ ልዩነት ተፈጥሮ ነበር።
የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደር (ካህናቱ) ወገንተኝነትን የያዙ በመሆናቸው የሃሳብ ልዩነቱን ማቀራረብም ሆነ ማስታረቅና መዳኘት ባለመቻሉ ጉዳዩ ተካሮ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከፍተኛ ሁከትና ረብሻ አስከተለ። ከዚህ በመቀጠል በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥ ያሉት ኮሚቴዎች ሁሉ በሚሳተፉበት ጥምር ጉባኤው ተሰብስቦ የመፍትሔ ሃሳብ እንዲያቀርብ ተደርጎ ሁለት አማራጮችን አቅርቦ ስለነበር ምርጫው ከመካሄዱ (ከ03-02-02013) በፊት ጠቅላላ ጉባኤው በቅድሚያ በጉዳዩ ላይ ተወያይቶበት አንዱን አማራጭ መርጦ እንዲወስን ከጉባኤው ቀን አስቀድሞ ብዙ ቁጥር ያላቸው አባላት ሕጋዊ ማመልከቻ (Petition) በመፈረም ለቤተ ክርስቲያኑ ጽ/ቤት አስገቡ፤ በቃልም ቀርበው አስረዱ።
በዕለቱ ስብሰባ ላይ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ግርማ ከበደና የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ ((Management Committee) አባላት የሆኑ ቄስ ዳዊት አበበና ቄስ አባተ ጎበና ስብሰባውን እንደከፈቱ ከአሁን በፊት በጥምር ጉባኤው የተወሰነውን ሁለት አማራጭ ሳያነሱና የአባላቱንም ማመልከቻ (Petition) ንቀው ወደጎን በመተው ምርጫውን በጉልበት እናካሂዳለን በማለት ሕዝቡን ማስገደድ ጀመሩ።
በስብሰባው ላይ አባላት ድምጻችን ይሰማ በማለት ከፍተኛ ትግል ካካሄዱ በኋላ ለመጠየቅና አስተያየት ለመስጠት ዕድል አገኙና በርካታ ሕጋዊ ጥያቄዎችን አቀረቡ። ከዚህም ጋር በማያያዝ ገንቢና ወደ ሰላምና አንድነትም የሚያመራ የበሰለ አስተያየት ሰጡ።
የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪና ሁለቱ ካህናት ግን የተጠየቀውን ጥያቄ ለመመለስም ሆነ የተሰጠውን አስተያየት ለመቀበል ፍቃደኛ ባለመሆኑ ምርጫውን እናካሂዳለን በማለት ቀጠሉበት። በዚህ ወቅት ሕዝቡ ተቃውሞውን በጩኸትና በመዝሙር ገለጸ። ካህናቱ የሕዝቡን ጥሪና አቤቱታ ከመስማት ይልቅ ልባቸውን እንደ ድንጋይ በማጠጠር ሕዝቡን ቀርቶ እግዚአብሔርንም ባለመፍራት ምርጫውን በኃይል እናካሂዳለን በሚል ቀጥለውበት ሕዝቡን በተቃዋሚና በደጋፊ ጎራ ተከፍሎ እንዲበጣበጥ መቀስቀስ ጀመሩ።
ይባስ ብለው የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ የተቃዋሚውን ሕዝብ ድምጽ በድምጽ ማጉያ ኃይል በመብለጥ አስቀድመው ያዘጋጇቸውን ተመራጭ እጮዎች ሥም ዝርዝር በመጥራት ጸሐፊውን መዝግብ እያሉ ምርጫውን ለማካሄድ ጣሩ።
የጌታችን የመድሃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስ ቃል ግን እንዲህ ይላል።
በእናንተ ዘንድ ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በውድ እንጂ በግድ ሳይሆን በበጎ ፈቃድ እንጂ፤ መጥፎውን ረብ በመመኘት ሳይሆን ጎብኙት፤ ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማህበሮቻችሁን በግድ አትግዙ፤ የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ። (1ኛ ጴጥ. 5፡ 2-4)
አስተዳዳሪው ሰውንም እግዚአብሔርንም አልፈራም ብለው በድርጊታቸው ሲቀጥሉበት ስብሰባው በሁከት ተሞላና ምንም መቋጫ ሳይደረግና ቀጣዩ ሁኔታ ሳይገለጽ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ስብሰባውን ዘግቻለሁ በማለት ለጸሎት ተነሱ አሉ።
ከጸሎቱ በኋላ ግን አባላት ከቤተ ክርስቲያናችን አንወጣም በማለት ስብሰባውን በመቀጠል በሕዝብ ተመርጠው የተሾሙት የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ቀደም ሲልም ሆነ በዕለቱ ያሳዩት ከአንድ መንፈሳዊ መሪና የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የማይጠበቅ አንባገነንነትና ሕዝብን ከሕዝብ የመከፋፈል ተግባርን በመገምገም በአስተዳዳሪው ላይ የVote of No confidence ለማካሄድ ሲል በስብሰባው ላይ ህጻናት፤ አቅመ ደካሞችና አዛውንቶች ሳይቀሩ እንደሚገኙበት እያወቁ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ የቤተ ከርስቲያኑን መብራት በማስጠፋት ሕዝቡን ለከፍተኛ አደጋ አጋለጡ።
ከዛም በሕዝቡ ጩከትና ተቃውሞ መብራቱ እንደገና እንዲበራለት ካደረገ በኋላ አባላቱ ስብሰባውን በመቀጠል በቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ላይ የጀመርውን Vote of No confidence በማካሄድ በውሳኔው ላይ ከተፈራረመ በኋላ በሚቀጥለው ሳምንት (በ10/03/2013) ከቅዳሴ አገልግሎት በኋላ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የጠቅላላ ጉባኤውን ስብሰባ ለማካሄድ ቀጠሮ ይዞ ተለያየ። ይህንንም የጉባኤ ውሳኔ ለሰበካ አስተዳደር ጉባኤው ጽ/ቤትና ለሚመለከተው ሁሉ አሳወቀ።
ጠቅላላ ጉባኤው የቀጠረው ስብሰባ ቀን እስከሚደረስ ባለው የአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ስልጣኔ ሊወሰድብኝ ነው ብለው የደነገጡት የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ከሌሎች በሥጋዊ ዓላማ ከሚተባበሯቸው ካህናት ጋር በመሆን የሰንበት ት/ቤት ወጣቶችና ሌሎችን በመቅረብ የተነሳውን የአስተዳደርና የሕዝብ መብት ጥያቄ የሃይማኖትና የቀኖና ጉዳይ አስመስሎ ሰፊ የሃሰት ቅስቀሳ በማድረግ የካህናቱን የሃሰት ቅስቀሳ አምነው የተቀበሉትንና ቤተ ክርስቲያኗ የምትከተለውን ገለልተኛ አቋም የሚቃወሙ የፓለቲካ ወገንተኞችን በማቀናጀት ለአመጽና ለረብሻ እንዲሰለፉ አደራጇቸው።
በዚህ መሠረት ነው በ10/02/2013 እሑድ ዕለት ከቅዳሴ አገልግሎት በኋላ የቤተ ክርስቲያኑ አባላት የጠቅላላ ጉባኤውን ስብሰባ ለማካሄድ ባስቀደሱበት ወንበር ላይ እንደተቀመጡ በቪድዮው ላይ የሚታየው የስድብ ናዳ የወረደባቸው።
በጸጥታ የተቀመጡት የቤተ ክርስቲያን አባላት የሆኑ አዛውንቶች፤ ጎልማሶችና ወንድና ሴቶች ሁሉ ዓላማቸው ሰላማዊና የመብት ጥያቄ ሲሆን የሚጠይቁትም ሆነ የሚቃወሙት የቤተ ክርስቲያኑን አስተዳደር እንጂ ከርስቲያን ወንድሞቻቸውን እህቶቻቸውንና ልጆቻቸውን ባለመሆኑ በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ እንደሚታየው የሚሰነዘርባቸውን ስድብ፤ ዛቻና ማስፈራሪያ ሁሉ በጸጋ ተቀብለውታል።
ሰው ናቸውና መናደድና መበሳጨት ቢኖርም መልስ ቢሰጡና ግብግብ ቢገጥሙ የሃይማኖታችውንና የቤተ ክርስቲያናቸውን ክብር ማስነካት ስለሚሆን ሁሉንም በእግዚአብሔር ፍቃድ ችለው አልፈውታል።
ተሳዳቢዎቹ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶችና ተባባሪዎቻቸው አስተዳደሩን ወግነው፤ ሕዝቡን መቃወማቸው ያልተለመደና ትርጉም የለሽ ቢሆንም በመቃወሙ ካመኑበት ግን መብታቸው ስለሆነ ሥርዓትን ጠብቀውና የሌላውን መብት ሳይጋፉ ተቃውሞአቸውን ማሰማት በቻሉ ነበር።
እንኳንስ ከርስቶስ በደሙ በዋጃት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቀርቶ በየትኛውም ቦታ የሌላውን መብት የሚጥስና፤ ሰብዓዊ ክብሩን የሚነካ ተቃውሞ ማካሄድ ምድራዊውም ሆነ ሰማያዊ ሕግ የሚፈቅደው አይደለም።
የጌታ ቃል ግን እንዲህ ይላል።
አንደበቱን ሳይገታ ልቡን እያሳተ፤ እግዚአብሔርን የሚያመልክ የሚመስለው ማንም ሰው ቢኖር የርሱ አምልኮ ከንቱ ነው (ያዕ. ፩፡ ፪፮)
3.1 በተንቀሳቃሽ ምስሉ መጀመሪያ ላይ የሚታየው በተራ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰውን የመጨረሻ ክንውን አነስተኛ ክፍል ቀንጭቦ የሚያሳይ ነው።
3.2 በቀጣዩ ላይ ያለው በቪዲዮው ላይ እንደተመለከተው በተራ ቁጥር 2 ላይ ያለውን አብዛኛውን ክንውን የሚገልጽ ነው።
3.3 በዚህ ቪዲዮ ላይ በግልጽ የሚታየው የሁከቱ ጠንሳሽ፤ አቀነባባሪና፤ አዝማች ከኋላ በኩል ጥቁር ቆብና የደፉና ነጭና ጥቁር የመነኩሴ ልብስ የለበሱ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ግርማ ከበደ ናቸው።
3.4 አንድ ምስል ከአንድ ሺህ ቃል የበለጠ ገላጭ ነው እንደሚባለው፤ ገና ከጅምሩ ስብሰባው አይካሄድም ብለው በድምጽ ማጉያ በመናገር ሁኩቱ እንዲጀመር መመሪያ የሰጡትና ሁከቱን ከኋላ ሆነው እየተንጎራደዱ ከማየት በስተቀር እንደ መንፈሳዊ አባት ልጆቼ አንተም ተው፤ አንቺም ተይ ሳይሉ በል ግፋ የሚሉት እኚሁ መነኩሴ ናቸው።
3.5 ሌላ የእኚሁ አስገራሚ መነኩሴን ሥራ በተንቀሳቃሽ ምስሉ ውስጥ እንመለከታለን፡ እሱም አንድ ጥቁር ካፓርት መሳይ የለበሰ ጠይም ሰው ስድቡና ጫጫታው ወደ በርከተበት ቦታ መጥቶ ነገሩን ለማረጋጋትና ለማበረድ ሲሞክር መነኩሴው ከኋላ ተንደርድረው በመምጣት ያ ሰው የሚያደርገውን የማረጋጋት ሙከራ ትቶ ወደ እሳቸው እንዲሄድ ልብሱን ነክተው ይጠሩታል። ይህ ምስል መነኩሴው ሁከትና ረብሻውን መቀጠሉን እንደሚፈልጉትና እሳቸው ቀርቶ ሌላም ሰው እንዲያበርደው እንደማይፈልጉ በግልጽ ያሳያል።
3.6 እዚህ ላይ ከሚታዩት ነገሮች ውስጥ ከምንም በላይ የሚያስገርመው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቀርቶ በየትም ሕግና ሥርዓት አለ በተባለበት ቦታ መነገር የሌለበትን ስድብና ማስፈራሪያ በሰዎች ላይ ሲወርድ መስማት ቢሆንም ከዛ ቀጥሎ ሌላውና እጅግ አስገራሚው ነገር ግን መሳደብ ቀርቶ ምንም ቃል ያልተነፈሰንና አርፎ የተቀመጠ ሰው ላይ ያለማቋረጥ የስድብ ናዳ ሲወርድበት ማየት ነው።
3.7 ስድቡን በተመለከተ ደግሞ እጅግ አስገራሚው ነገር ከተሰነዘሩት ስድቦች፤ ዘለፋዎችና ማስፈራሪያዎች ውስጥ ታናሽ፤ ታላቁን፤ ልጅ አባቱና እናቱ የሚሆኑ አዛውንትና ባልቴቶችን ቀርቶ ክርስቲያን ክርስቲያኑንም ሆነ ማንም ሰብዓዊ ፍጡር ሌላውን ሰብዓዊ ፍጡር ሊሰድበው የማይገባውን ስድብ ሲሳደብ የነበረው ሰው ከሰንበት ት/ቤት ወጣትነትም በላይ ዲያቆን መሆኑ ነው።
3.8 ይህ iPod ይዞ ምስል የሚቀርጽ ሰው ዲያቆን ሲሆን ይህም ሰው አዕምሮው ያልበሰለ ህፃን ወይም (Tin age) ሳይሆን በሠላሳዎቹ ዕድሜ ውስጥ ያለ ጎልማሳና ነገሮችን ለማመዛዘን የሚያስችል ዕድሜ ላይ የደረሰ የተሟላ ሰው ሆኖ የሚያወርደው እጅግ ዘግናኝ ስድብ ግን ከሁሉም የከፋ ነው።
3.9 ይህ የከፋውንና የሚሰቀጥጠውን ስድብ ሲሳደብ የነበረው አንድ ዲያቆን ይሁን እንጂ በስድቡ ውስጥ ተሳታፊ የሆነ ሌላ ዲያቆንም አለ። ይህም ዲያቆን የሁለት እጆቹን ሁለት ጣቶች በማውጣት በማሾፍ መልክ ወደ ቪዲዮው ቀርቦ የተቀረጸው ወጣት ነው።
3.10 ዲያቆናትን አስመልክቶ የሃይማኖታችንና የቤተ ክርስቲያናችን ሕግ ቀጥሎ የተመለከተውን የሚል ሲሆን ይህንን ከዲያቆናቱ ድርጊት ጋር በማመዛዘን ለመረዳት ፍርዱን ለተመልካች ትተነዋል።
3.11 ዲያቆናት ጸጥ ያሉ፤ የሚታዘዙ ይሁኑ፤ በሁለት አንደበት አይናገሩ፤ ቁጡዎች አይሁኑ፤ቁጣ አዋቂውንም ሰው ያጠፋል (ረስጣ ፩፯ ጤት ፬)
3.12 ዲያቆናት መልካም ሥራን በመዓልትም በሌሊትም፤ በቦታው ሁሉ የሚሠሩ ይሁኑ፤ ያለ ኃጢዓት በጎ ማገልገልን ያገለገለ ይህ ይጠቅማል፤ በጎ ድርሻንም ይቀበላል። (ፍትሐ ነገሥት)
3.13 በቪድዮው ላይ ከሚደመጠው ስድብ የከፋውንና ጆሮ ሰምቶ ለመቀበል የሚያዳግተውን ድቁናን በተቀበለ ሰው አንደበት የተነገረ በመሆኑ ተጠቀስ እንጂ አብዛኞቹ ስድቦች ያነጣጠሩት በአዛውንቶችና የዕድሜ ባለጸጋ በሆኑ ሰዎች ላይ ነበር።
3.14 አብዛኛዎቹ እነዚህ አዛውንቶችና ጎልማሶች ደግሞ በስደት ሃገር ከተመሠረተች 40 ዓመታትን ባስቆጠረችው ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አስር፤ ሃያ፤ ሰላሳና ከዛም በላይ ዓመታት እንደውም አንዳንዶቹ ተሳዳቢዎች ሳይወለዱ ጀምሮ የኖሩና ያገለገሉ ናቸው።
3.15 ክርስቲያን ማለት የክርስቶስ ምሳሌ የሚሆንና የክርስቶስን መንገድ የሚከተል ማለት ነው። እንዴት ብሎ ታላቁን፤ የሚወልደውንና አንዳንዱም አያቱ የሚሆነውን አዛውንት ምንም ሳይለው እየሰደበና እያዋረደ መልሶ እኔ ክርስቲያን ነኝ ሊል ይችላል?
3.16 እንዴትስ ካህናትና የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መነኩሴ ሰውን ቀስቅሶና አደራጅቶ ይህን መሰል ድርጊት እንዲፈጸም ያደርጋል? ድርጊቱ ሲፈጸምስ እያየስ በጭካኔ ዝም ብሎ ካሳለፈ በኋላ ተመልሶ እኔ ከእግዚአብሔር ጋር የማገናኝ ድልድይ ነኝ በማለት ለመናገር የሚችል ሂልና ሊኖረው ይችላል?
ወስብሐት እግዚአብሔር!! አሜን።
© 2013, ↑ Ethiopian News in Amharic
Log in- Posts - Add New - Powered by WordPress - Designed by Gabfire Themes
Tadesse Ketema
March 15, 2013 at 9:23 am
Brothers sisters and all of Orthodox Christians, please pray for all Orthodox churches , the same problem in Ireland,Dublin, Debrework Mariam as well.We have only one church in Ireland, we have few members,economically poor church………….but strong,committed, ”Yesebeka Gubae” members. Please God help your people.
tazzachen
March 13, 2013 at 9:21 am
ewnet yezegeyal enji mewtatu aykerm ande ababale ale YEMITAYEBETEN AMELEKAKET KEYERE ENJI YEMITAYEBETEN AYENE ATECHEFEN yebalale.enga ethiopians ye sewn metfo tegebar tolo yemagalet dikmet alebin leban leba weshetamen weshetam kalalut eyadege siree eyeseded yemetale ahunem bebetekiristaniyachen wieiste yegetemen chiger kemegemeryaw akfen debiken yeyaznachew metfo tegebarachewn eyayen egziabher yeker yebelachew eyalen alfnew. egziabher hule besew temeslo new hulun yemiseraw ahunem yehen bete mekdesachenen yarekesuten ye BEGE LEMED YELEBESUTEN TEKULAWOCH mastdate alben yale minme tiriter yestdalu. ande tiyake lesenbet temariwoch ena ledikonat kifu ke afachu lewta ewnet be awde miheretu lay endezih abatochen mesadeb ke yet yemeta kirestna new? yegiziabher kale enatena abatachun talakihne akber new yemilew yhe new kiristna ?ewnetegna kidus menfes be enaneteme abatachen bilachu beemitaleksulet aba girma endih sitisadebu aygebam newre new ke afachu metfo ayewta bilo aygetsem wendemoch ehtoche esti ye abane fiker endale yazutena be mehalachu yemiseruten metfo sira bedenbe astewelu ergetegna nege bizu yemitawkut guday ale sele ewnet mekomu tiru new SEWEN atfiru mefrat EGZIABHEREN new ene be bekule (aba) yemilewn le ewnetegna abte yemisetewen kiber le girma letenkolegna bekifate letemola menekuse nege baye be mehalachen metfo tegebarena erkuse menfesen mekefafelen lemizera sew ye abatenet tegbare lelelew aygebawem.
Abiy Ethiopiawi Segawi/wemenfesawi አቢይ ኢትዮጵያዊ ሥጋዊ-ወመንፈሳዊ
March 11, 2013 at 8:19 am
***መራራቁ ነው ችግሩ***
አቤት ውሽት???
አቤት ቅጥፈት???
“ዲያቆናት??
እኛ አባት???”
ማን ይመስክር የነበረ:
አንጀታችን እያረረ…
በእምዬ ደጅ ባማላጇ
በታቦቷ በቀኝ እጇ
በበረከት ያፈራችው የእሷው መቅደስ
በአዛውንቶች ሲደፈር በኅጣኖች ሲታመስ
በብሌኗ በዓይናችን ጉዱን አይተን”እግዚኦ!”ስንል
ከየት መጣ አባግርማን
የሚያዘልፍ ቀልብ የሚያስጥል????
እኛ ነበርን”ምንቲ”የሚሏት ስታዳምቅ ተደባልቃ;
ይልቅ መፍትሔ ብትፈልግ አይሻልም ሐቁን አውቃ???
እረ!!!ወገን እንፀልይ እንድ’ነቃ
በሰይጣን ልብ ማሰቡ
ዛሬውኑ እንዲያበቃ::
በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አንድ ጉባኤ ይጠራና
ተሰብስበን እንወያይ ችግሩ ሁሉ ይብራራና::
እባካችሁ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ቤት ስለሆነች
በልባችን ክፋት ይዘን ለሰይጣኖች ተዉ አንመች::
አባ ግርማም ቢሆኑ ዕውነት መናገር አይፈሩ
ምዕመናንም ይጠሩና በኮሚኒቲው ይናገሩ::
መደባበቅ አያሻንም ይጠየቁ እንዲያብራሩ
ኮሚኒቲው ሚና ኖሮት
አሁኑኑ ሕዝቡን ይጥሩ::
እኔ እንዳየሁት ነገሩ:-
መራራቁ ነው ችግሩ::
SOLO
March 10, 2013 at 10:25 pm
yemigerm new atefered yeferedebehal new negeru atersu …who gave you the right to blame and support others , God will eventually clean his house , not woyane , ginbot 7 or esat ,,,
Ewunet
March 10, 2013 at 5:20 am
Betam betam yemiyasaznena mamen yemiyaket dergit newu yemitayeu yediyakonochu bicha sayehon yesetochu huneta erasu betam asafari newu lemematat yemimeesu endalhone kehunetachew yastawukal yehe betam asafari yehone serachewu ketarik eskzelaem ayetefam egzio yemiyaseg newu krestiyanawi tegbarem ayedele min ayenet astedadeg bihon newu setu wendu endih ashakbo talaakochun yemisadeb enesu endih yehonu minabat yeleg enatoch kehonu lelegochachewu min ayenet araya lihonuachewu newu mehal lemehal eyetengoradede yemisadebewu Fasil erasu leregim gize yemiyawukachewun azawunt abatoch alemaferu endeziya sinager mamen newu yemiyaketewu wuha wede elay yefesal malet yehenewu kalu eko yemilewu Abatena Enatehen akber eng awared ayedelem tadiya krstiyanenetu minu laye newu Aba Girma ema leseletanachewu engi ybetekiresetiyanum hone yehayeminotu huneta ayasasebachewum tikimachewu endayekerebacheu enge yegize gudaye kalhone besteker megaetachewu ayekerm.