አቤ ቶኪቻው
ላለፈው አንድ ወር አካባቢ የጠቅላይ ሚኒስትሩ “ግባተ መሬት” እስኪፈፀም ድረስ እንዲሁም መንግስት ሀዘኑ በረድ እስኪልለት እና ለቀስተኛ እንግዶች እስኪሸኙ በሚል ጋብ ብሎ የነበረው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ሰላማዊ ጥያቄ በዛሬው ዕለት በርካታ አማኞች በተገኙበት በአንዋር መስጊድ ተከናውኗል።
ሙስሊም ኢትዮጵያውያኖቹ በዛሬው የተቃውሞ ውሏቸው የታሰሩ በርካታ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እና ኡስታዞች እንዲፈቱ እንዲሁም በቀበሌዎች ሊደረግ የታሰበው የመጅሊስ ምርጫ ዕውቅና የማይሰጡት መሆኑን ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ገልፀዋል።
ልብ አድርጉልኝ 1
አነዚህን ወንድሞቻችንን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቅሶ ቀለል እኪል ብለው የወሰዱት የስክነት እርምጃ የሚደነቅ ነው። እነዚህን ወንድሞች ነው እንግዲህ መንግስት ባለፈው ግዜ “ሆን ብላችሁ የአፍሪካ ህብረት ስብሰባን ለማወክ አስባችኋል” ብሎ በአስለቃሽ ጭስ እና በአስለቃሽ ዱላ እየዬ ሲያስብላቸው የነበረው። ታድያ ብዙ መራቂ አባቶች አሉን አይደል እንዴ “እንዳስለቀሳችሁን እርሱ ያስለቅሳችሁ” ብለው መንግስታቸውን መረቁ… አፍታም አልቆየ ወድያውኑ የመንግስት ዋና ዋና ሰዎች እየዬ አሉ።
ልብ አደርጉልኝ 2
አሁንም ብዙሃኑን ጥቂት ማለት አደጋው ብዙ ነው። እናም መስማት ይበጃል። አለበለዛ ማለቅስ ይመጣል… “ጥንቱን ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማለቀስ” ይል ነበር አባቴ… እናም የመንግሰት ዋና የስራ ሂደት ባለቤቶች ሆይ እባካችሁ መጥናችሁ ደቁሱ…!
የቃላት መፍቻ
በዚህ ወግ አግባብ “መደቆስ” ተብሎ የተገለፀው ችግሮችን ለመፍታት የሚደረግ የሰለጠነ ዘዴ ነው። እደግመዋለሁ መንግስታችን ሆይ አሁንም ባለችው ጊዜ እባክህ መጥነህ ደቁስ…!
ዘግይቶ በደረሰኝ ዜና ፖሊስ ዛሬም በደሴ ሙስሊም ምዕመኑን ሲደበድብ ውሏል። ይህ አይነቱ “መደቆስ” ይዳርጋል ለማልቀስ…! ተዉ ልብ ግዙ….! የልብ ገበያ የት እንደሆነ እንጠቁማለን…!
© 2012, ↑ Ethiopian News in Amharic
Log in- Posts - Add New - Powered by WordPress - Designed by Gabfire Themes
belachew
September 21, 2012 at 7:49 pm
Abe min godelebeih. Bicha le machester feremish aydel. Bilatbilt.